2026 የሲያትል የትራንስፖርት መለኪያ እድሳት (STM)
This content has been professionally translated in other languages.
Este contenido ha sido traducido profesionalmente a otros idiomas.
此內容已被專業翻譯成其他語言。
Nội dung này đã được dịch chuyên nghiệp sang các ngôn ngữ khác.
Qoraalkan waxaa si xirfad leh loogu turjumay luqado kale.
ይህ ይዘት በሙያዊ በሌሎች ቋንቋዎች ተተርጉሟል።
የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ ኅዳር 2026 የምርጫ ወረቀት ላይ ይካተታል። በመራጮች ከጸደቀ፣ የ2026 ሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ከተማዋ ለ10 ዓመታት የ0.3% የሽያጭ ታክስ እንድትሰበስብ ስልጣን ይሰጣታል፣ ይህም በቀን ውስጥ በማንኛውም ጊዜ የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎትን ለማሻሻል፣ የሕዝብ ማመላለሻ ተደራሽነትን ለመጨመር፣ እንዲሁም ሰዎችን ከተለያዩ እድሎች ጋር በማገናኘት የዕለት ተዕለት የጉዞ ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት ያስችላል።
ከእኛ ጋር ይገናኙ። ለእርስዎ ማህበረሰብ ስብሰባ ወይም መገናኛ የመረጃ ማብራሪያ ለማግኘት ወይም ጥያቄዎችን ለመጠየቅ በ STM@seattle.gov ኢሜይል ይላኩልን።
በዚህ ገጽ ላይ:
- 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት
- ይህ እድሳት በሲያትል የግብር ከፋዮችን ምን ያህል ወጪ ያስከትላል?
- የ 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ሂደት
- 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት አካላት
2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት
ከንቲባ ዊልሰን፣ የ2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳትን በኅዳር 2026 በሚካሄደው ምርጫ ለመራጮች ለማቅረብ የሚያስችለውን ሕግ ሐምሌ 30 ቀን ፈርመዋል። ሕጉ በከተማ ምክር ቤት በ9-0 ድምፅ ጸድቋል።
የ2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት (STM)፣ በቀኑ በማንኛውም ሰዓት የማጓጓዣ አገልግሎትን ለማሻሻል እና ተደራሽነትን ለመጨመር፤ እንዲሁም ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገናኘት የዕለት ተዕለት የጉዞ ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት የሚውል ለ10 ዓመታት የሚቆይ የ0.3% የሽያጭ ታክስ ነው።
- 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት – በምክር ቤት የፀደቀው ደንብ
- 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት – በምክር ቤቱ የፀደቀ ማጠቃለያ እና የፋይናንስ ማስታወሻ
የ2026 የSTM እድሳት፣ ለመጓጓዣ ሥርዓታችን የወደፊት ሁኔታ የተቀረጸ የ20 ዓመት ራዕይ ከሆነው ከሲያትል የመጓጓዣ ዕቅድ ጋር የሚጣጣም እና እሱን የሚደግፍ ነው። በተለይም የመኪና ባለቤት መሆንና የመጠገን ወጪ እየጨመረ በመምጣቱ፣ የሲያትል ነዋሪዎች ለጉዟቸው ይበልጥ ተመጣጣኝ ዋጋ ያለው እና አስተማማኝ አማራጭ የሆነውን የሕዝብ ማመላለሻ መጠቀም እንደሚፈልጉ ገልጸውልናል።
የሲያትል መራጮች ካጸደቁት፣ የ2026 የSTM ማደሻ ጊዜው የሚያበቃውን የ2020 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት እርምጃ ይተካል። የ2020 STM በ0.15% የሽያጭ ታክስ የሚደገፍ እና በመራጮች የጸደቀ የ6 ዓመት ዕቅድ ነው። የሚያበቃው የ2020 STM እስከ ሚያዝያ 2027 ድረስ የሕዝብ ማመላለሻ መዋዕለ ንዋዮችን ለመደገፍ በየዓመቱ ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያመነጫል። አሁን ባለው የ2020 STM ስለተደረጉ መዋዕለ ንዋዮች የበለጠ ለማወቅ የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ድረ-ገጽን ይጎብኙ።
የ2026ቱ የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት የሚከተሉትን በገንዘብ ለመደገፍ ያለመ ነው፦
- በየዓመቱ በሲያትል 275,000 የአውቶቡስ ጉዞዎች፣ አሁን ካለው በ95,000 የሚበልጡ ጉዞዎች
- በቀን ለ24 ሰዓታት፣ በሳምንት ለ7 ቀናት የተሻለ የአውቶቡስ አገልግሎት። ይህ ማለት ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም ሰዎች በብዛት ከሚንቀሳቀሱባቸው የተለመዱ ሰዓቶች ውጪ፣ በቀን መሃል እና በሌሊት የሚደረጉ ተጨማሪ ጉዞዎች ይኖራሉ ማለት ነው።
- በሕዝብ ማመላለሻ ላይ በብዛት የሚተማመኑትን ሕዝቦች ለማገልገል ቀጣይ ትኩረት
- በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎች፣ አረጋውያን እና ትናንሽ ልጆች ያላቸው ቤተሰቦች የሕዝብ ማመላለሻ ለመጠቀም ያለውን መሰናክል ለመቀነስ ለ22,000 ሰዎች ነፃ የORCA ካርዶች
- ለአካባቢው ቦታዎች፣ ለሥራዎች፣ ለትምህርት ቤቶች፣ እና ለክልላዊ ቀላል ባቡር አውታረ መረብ መዳረሻ ለሚሰጡ ለሁለቱ የሲያትል የመንገድ መኪና መስመሮች
- አውቶቡሶች የሚዘገዩባቸው ቦታዎች ላይ የጉዞ ጊዜን ለመቀነስ እና አስተማማኝነትን ለማሳደግ የተመረጡ የግንባታ ፕሮጀክቶች
- ቀላል ባቡርን በፍጥነት እና ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ለመገንባት ፈቃዶችን እና የግንባታ ቁጥጥርን ማፋጠን፣ እንዲሁም የግራሃም ስትሪትን (Graham Street) እና የሳውንድ ትራንዚት ዌስት ሲያትል (Sound Transit's West Seattle) እና የባላርድ ሊንክ ኤክስቴንሽን (Ballard Link Extension) ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የወደፊት ጣቢያዎች ተደራሽነትን ማሻሻል
የ2026ቱ የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት አገልግሎት እርምጃ በዓመት በግምት $138 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኛል። ከዚህ ውስጥ 86 በመቶው ለሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት የሚውል ይሆናል።

የ2026 የSTM እድሳት በአማካይ በየዓመቱ ወደ $138 ሚሊዮን ዶላር ያሰባስባል። ይህም ከገንዘቡ 86 በመቶውን ለሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት (ለአውቶቡስ አገልግሎት $94.6 ሚሊዮን ዶላር፤ ለሲያትል ስትሪትካር (Streetcar) $23.4 ሚሊዮን ዶላር) ይመድባል፤ ቀሪው ድርሻ ደግሞ ለሕዝብ ማመላለሻ ተደራሽነት ፕሮግራሞችና ለትምህርት ($9 ሚሊዮን ዶላር)፣ ለ"Sound Transit 3" ፕሮጀክቶች የሚደረግ የከተማው ድጋፍ ($6.1 ሚሊዮን ዶላር) እንዲሁም ለታለሙ የሕዝብ ማመላለሻ መሠረተ ልማቶች ($5 ሚሊዮን ዶላር) ይውላል።
ለሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት የሚውል እያንዳንዱ የSTM ዶላር፣ የሜትሮን የደህንነት ጥረቶች በመደገፍ እንዲሁም ተደጋጋሚ እና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲኖር በማድረግ የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎቱን ደህንነት ለማሻሻል ያግዛል። በተጨማሪም፣ ተጨማሪ አውቶቡሶች እና አጭር የጥበቃ ጊዜ ሲኖር ለሁሉም ሰው ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ ጉዞ ማለት ነው።
ይህ እርምጃ በሲያትል ግብር ከፋዮች ላይ ምን ያህል ወጪ ያስከትላል?
ይህ ጊዜው ሊያበቃ ለቀረበው የ2020 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ (STM) እንደ ምትክ የቀረበ ሐሳብ ነው። ከ2020 ጀምሮ ወጪዎች ጨምረዋል፤ እንዲሁም ፍላጎቶች እና የሕዝብ ማመላለሻ ተጠቃሚዎች ቁጥር አድገዋል። በዋሽንግተን ስቴት ሕግ ሥር፣ የሽያጭ ታክስ ከተሞች የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎትን ለመደገፍ ሊጠቀሙባቸው ከሚችሏቸው ጥቂት የገቢ ምንጮች አንዱ ነው። የ10 ዓመት የ2026 የSTM እድሳት በስቴቱ ሕግ የሚፈቀደውን ረጅሙን የጊዜ ገደብ የሚሰጥ ሲሆን፣ ከተማዋ አገልግሎቶችን ለማቀድ እና ለማቅረብ የሚያስችል የተሻለ መረጋጋት ይሰጣታል።
በዓመት $121,000 የሚያገኝ ሁለት ሰው ያለው አማካይ የሲያትል ቤተሰብ፣ የዓመታዊ ወጪው በግምት $58፣ ወይም በወር $4.83 እንደሚሆን ይጠበቃል። ይህ አማካይ የሲያትል ቤተሰብ ዛሬ ለSTM ከሚከፍለው በዓመት በ$29 ይበልጣል። 30% የአማካይ ገቢ ወይም በዓመት $38,000 የሚያገኝ ዝቅተኛ ገቢ ያለው ቤተሰብ በግምት $35፣ ወይም በወር $2.91 ይከፍላል ተብሎ ይጠበቃል።
የ 2026 የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ሂደት
የ2026ቱ የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት የተዘጋጀው፣ የተለያዩ ፕሮግራሞችን እና አገልግሎቶችን በተመለከተ ከሕብረተሰቡ በተገኙ አስተያየቶች ላይ በመመሥረት ነው፤ ከእነዚህም መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል:
- ሕዝባዊ የዳሰሳ ጥናቶች
- በማህበረሰብ ዝግጅቶችና ስብሰባዎች ላይ የማህበረሰብ ተሳትፎ
- ከፕሮግራም አጋሮች እና ተሳታፊዎች ጋር ውይይቶች
- ከሕዝብ መጓጓዣ አማካሪ ቦርድ እና ከመጓጓዣ ፍትሃዊ እኩልነት የስራ ቡድን ጋር የሚደረጉ መደበኛ ውይይቶች
- የሲያትል የመጓጓዣ ዕቅድ ዝግጅት ሂደት አካል ከሆነው ጥልቅ ተሳትፎ የተገኙ ውጤቶች
ይህ ግብዓት የሲያትል ነዋሪዎች በሚከተሉት ዘርፎች ኢንቨስት እንድናደርግ እንደሚፈልጉ አሳይቶናል፦
- በቀኑ ሁሉም ሰዓቶች፣ በተለይም በመሃል ቀን፣ በማታ፣ በሌሊት እና በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት፣ ይበልጥ ተደጋጋሚ የአውቶቡስ አገልግሎት
- በሕዝብ መጓጓዣ አገልግሎት ላይ በብዛት ለሚተማመኑ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ተሳፋሪዎች፣ ከክፍያ ነፃ የሆኑ የአገልግሎት መርሃ ግብሮችን በማስፋት የመንቀሳቀስ አቅማቸውን ማሻሻል
- አውቶቡሶችን የበለጠ አስተማማኝ ማድረግ እና የጉዞ ጊዜን ማሻሻል
- ለአውቶቡስ ተሳፋሪዎችና ሾፌሮች ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢ መፍጠር
- እየሰፋ ካለው የቀላል ባቡር ኔትወርክ ጋር ግንኙነቶች
- ከዚህ የሽያጭ ታክስ የሚገኘው ገቢ በቀጥታ በጣም ተጽዕኖ የተፈጠረባቸውን ሰዎች እንዲጠቅም የሚያረጋግጡ ፕሮግራሞችና አገልግሎቶችን ማስፋት
የሲያትል ከተማን የዘር እና ማህበራዊ ፍትህ ድንጋጌ (Race and Social Justice Ordinance) መሠረት በማድረግ፣ የ2026 የSTM እድሳት ሐሳብን የማዘጋጀት አካል የሆነውን የዘር ፍትሃዊ እኩልነት መመሪያ ጥቅል (Racial Equity Toolkit) አጠናቀናል፣ ይህም እድሳቱ ተመጣጣኝ ዋጋ ባለው እና አስተማማኝ የማመላለሻ አገልግሎት ተደራሽነት ረገድ የሚታዩ የዘር ልዩነቶችን የማስወገድ የሲያትልን የረጅም ጊዜ ግብ እንዲደግፍ ለማረጋገጥ ያለመ ነው።
ከንቲባ ዊልሰን የ2026ቱን የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ሐሳብ በሰኔ 2026 ይፋ ያደረጉ ሲሆን፣ ሐሳቡም በሲያትል ከተማ ምክር ቤት በተመረጠ ኮሚቴ አማካኝነት ተገምግሞ ማሻሻያ ተደርጎበታል።
- የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ሐሳብ - ድንጋጌ
- የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት አቅርቦት - ማጠቃለያ እና የፋይናንስ ማስታወሻ
- የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት ሐሳብ - የዘር ፍትሃዊ እኩልነት መመሪያ
የ2026 የSTM እድሳት አካላት
የሕዝብ እንቅስቃሴን የሚያስቀጥል የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት (በዓመት በአማካይ $118 ሚሊዮን ዶላር)
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍ ይቀጥላል:
- ሲያትል ውስጥ፣ ኪንግ ካውንቲ ሜትሮ (King County Metro) በአሁኑ ወቅት ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ፣ በዓመት ወደ 175,000 የሚጠጉ ተጨማሪ የአውቶቡስ ጉዞዎችን በማከል የአውቶቡስ አገልግሎት ድግግሞሽን ማሳደግ
- በማታ፣ በሌሊት፣ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት እና በቀን መሃል በብዛት ለሚመጡ አውቶቡሶች
- ከተለመደው ወግ ውጪ ለሆኑ የመጓጓዣ አማራጮች እንዲሁም ለዝግጅቶች፣ ለምሽት መዝናኛዎች እና ለተለያዩ ጉዳዮች ለሚደረጉ ጉዞዎች ድጋፍ ማድረግ
- ሁለቱም የሲያትል ስትሪትካር (Streetcar) መስመሮች:
- የካፒቶል ሂል (Capitol Hill)፣ ፈርስት ሂል (First Hill)፣ የስለር ቴራስ (Yesler Terrace)፣ ሴንትራል ኤሪያ (Central Area)፣ ቻይናታውን-ኢንተርናሽናል ዲስትሪክት (Chinatown-International District) እና ፓይነር ስኩዌር (Pioneer Square)ን የተለያዩና ህያው የመኖሪያ ሰፈሮች እንዲሁም የንግድ አካባቢዎች የሚያገናኘው የፈርስት ሂል (First Hill) መስመር። ይህ አገልግሎት በከተማዋ ውስጥ ፍትሃዊ እኩልነት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው አካባቢዎች መካከል ለአንዳንዶቹ፣ እንዲሁም ለዋና ዋና የሕክምና ማዕከላት እና ለአካባቢው ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት ይሰጣል።
- የ South Lake Union መስመር፣ በሲያትል ታዋቂ መድረሻዎችን ማለት የአካባቢ ፓርኮችና ሙዚየሞች፣ የሕክምናና የምርምር ተቋማት፣ እንዲሁም ዋና ዋና ቀጣሪዎች እና የመሳሰሉትን ያገናኛል።
- የሜትሮ የደህንነት መዋዕለ ንዋዮች በማመላለሻ አገልግሎት ግዥዎቻችን በኩል፣ እንደ የባህሪ ጤና ባለሙያዎች እና የመጓጓዣ ደህንነት ኃላፊዎች ካሉ የሰለጠኑ ሠራተኞች ጀምሮ እስከ የአሽከርካሪዎች ክፍልፋዮች እና ከሜትሮ ክልላዊ የሕዝብ ማመላለሻ ደህንነት ግብረ ኃይል የሚመጡ ሌሎች መዋዕለ ንዋዮችን ጨምሮ በሁሉም ነገር ላይ ኢንቨስት ያደርጋሉ።
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍን ይጨምራል:
- በየሳምንቱ ከ50,000 በላይ ተጨማሪ ሰዎች በአውቶቡስ እንዲጓዙ ለማገዝ፣ በዓመት 95,000 ተጨማሪ የአውቶቡስ ጉዞዎች
የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ የመላው ሲያትል የአውቶቡስ አገልግሎትን በገንዘብ ይደግፋል
የ2026ቱ የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ መለኪያ እድሳት፣ በአሁኑ ወቅት ከሚያቀርባቸው የSTM 180,000 የአውቶቡስ ጉዞዎች በተጨማሪ በዓመት ተጨማሪ 95,000 የአውቶቡስ ጉዞዎችን ይጨምራል። እነዚህ ካርታዎች የ2020 STM በአሁኑ ወቅት ተደጋጋሚ የአውቶቡስ አገልግሎት የሚደግፍባቸውን ቦታዎች፣ እንዲሁም ተጨማሪ ጉዞዎች የሕዝብ ማመላለሻ አውታረ-መረቡን ሊሻሻሉ የሚቻልባቸውን ቦታዎች እንደ ምሳሌ ያሳያሉ። ቀን ሙሉ፣ ማለትም ከሰዓት፣ ምሽት፣ ሌሊት እና ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ተደጋጋሚ የትራንስፖርት አገልግሎት ማቅረብ ዋና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ይሆናል።
ይህ ምሳሌ ብቻ ሲሆን፣ በ2026 የSTM እድሳት ሐሳብ ሥር የታቀዱትን ትክክለኛ መዋዕለ ንዋዮችን አያሳይም።

የሕዝብ ማመላለሻ መዳረሻ ፕሮግራሞች (በአማካይ $9 ሚሊዮን በዓመት)
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍ ይቀጥላል:
- ለ10,000 ሰዎች ሙሉ በሙሉ በድጎማ የሚቀርቡ የሕዝብ ማመላለሻ ማለፊያዎች፤ የሚከተሉትን ጨምሮ:
- ሲያትል የቤቶች ባለስልጣን ነዋሪዎች፣
- ሲያትል ፕሮሚስ ስኮላሮች (Promise Scholars)፣ እና
- ከትምህርት ክፍያ ነፃ የሚማሩ የሲያትል መዋዕለ ህፃናት ፕሮግራም (Seattle Preschool Program) ቤተሰቦች
- ከትራንስፖርት ጋር የተያያዙ ሙያዎችን ግንዛቤ ለማስፋት ለወጣቶች የመጓጓዣ ትምህርት ፕሮግራሞች
- አረጋውያን በክልሉ የሕዝብ ማመላለሻ ሥርዓት ላይ ያላቸውን መተዋወቅና የመጠቀም ምቾት ለማሳደግ የታለሙ የሕዝብ ማመላለሻ ትምህርት ፕሮግራሞች
- የነዋሪዎችን ፍላጎቶች እና የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት የማግኘት እንቅፋቶችን ለመረዳት የሚደረግ ጥናት
- ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ለሚንቀሳቀሱ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተሳፋሪዎች አገልግሎት የሚሰጥ የአጭር መስመር አመላላሽ (Easy Loop ሻትል)
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍን ይጨምራል:
- የመንግሥት ድጋፍ በሚሰጥ መኖሪያ ቤት ውስጥ ለሚኖሩ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እና ለአብዛኞቹ የሲያትል ነዋሪዎች አገልግሎት ለመስጠት፣ 12,000 የቤት ምርጫ የቅናሽ ደረሰኝ የ"Housing Choice Voucher" ተጠቃሚዎችን የሚያካትተው የሲያትል መኖሪያ ቤት ባለስልጣን (Seattle Housing Authority) አጋርነት ማስፋፋት
የመጓጓዣ መሠረተ ልማት (በዓመት አማካይ $5 ሚሊዮን)
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍ ይቀጥላል:
- የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት በታቀደለት ጊዜ እንዲከናወን እና የተሳፋሪዎች የጉዞ ጊዜ እንዲሻሻል የሚያግዙ ፕሮጀክቶች፤ እነዚህም የአውቶቡስ አገልግሎት አስተማማኝነትን፣ ተደራሽነትን፣ ፍትሃዊ እኩልነትን እና ደህንነትን ለማሻሻል በሲያትል የማጓጓዣ ቀረጥ (Seattle Transportation Levy) አማካኝነት ከተደረገው የ$27 ሚሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ በመነሳት፣ በተለይም በርካታ መስመሮች ላይ ተጽዕኖ በሚያሳድሩ የአፈጻጸም ማነቆዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ናቸው።
- መዋዕለ ንዋዮች እንደ አውቶቡስ መስመሮች እና የምልክት ሥርዓት ማሻሻያዎች ያሉ የአገልግሎት አስተማማኝነትን የሚያሳድጉ ስራዎችን፣ እንዲሁም እንደ አውቶቡስ ማቆሚያዎች እና የመብራት አገልግሎቶች ያሉ ተደራሽነትን የሚያሻሽሉ መገልገያዎችን የመሳሰሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ይደግፋሉ።
ከተማ ለ Sound Transit 3 ድጋፍ (በአማካይ በዓመት $6.1 ሚሊዮን ዶላር)
ለሚከተሉት የገንዘብ ድጋፍ ይቀጥላል:
- ቀላል ባቡርን በፍጥነት እና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመገንባት የፈቃድ እና የግንባታ ቁጥጥርን የሚያፋጥኑ የከተማው ሠራተኞች፣ በዛውም ለወደፊት ጣቢያዎች በተለይም ለGraham Street ጣቢያ እና በሳውንድ ትራንዚት ዌስት ሲያትል (Sound Transit's West Seattle) እና Ballard Link Extension ፕሮጄክቶች ተደራሽነትን ማሻሻል።
- እስከ 10 የሚደርሱ ራሳቸውን የሰጡ የሙሉ ጊዜ የፕሮጀክት አስተዳደር ሠራተኞች፣ እቅድ፣ ምህንድስና፣ ፈቃድ እና የአካባቢ ግምገማን የሚያካሂዱ ሠራተኞች፣ ይህም ከተማዋ የሳውንድ ትራንዚት አጋርነት ዶላሮችን የመጠቀም አቅም በሚዛን እንድትይዝ ያስችላታል
- የሲያትል የሕዝብ ማመላለሻ ተጠቃሚዎች/ ተሳፋሪዎች ወደተስፋፋው የቀላል ባቡር መስመር አውታረ መረብ የሚያደርጉትን ጉዞ ለማሻሻል የሚያግዙ እንደ የእግረኛ መንገዶች፣ የተሻሻሉ የመንገድ መሻጋገሪያዎች፣ ለእግረኞች ምቹ የሆነ የመንገድ መብራት፣ የብስክሌት መንገዶችና ማቆሚያዎች፣ እንዲሁም የተሻሻሉ የአውቶቡስ ማቆሚያዎች ያሉ የካፒታል ፕሮጀክቶች ማቅድ እና ቅርጽ ማስያዝ
- ተመጣጣኝ ካልሆኑ ተጽዕኖዎች ለመቆጠብ እና ለሁሉም ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ወሳኝ የዘር ፍትሃዊ እኩልነት ውጤቶችን ጨምሮ፣ የከተማዋን እና የማህበረሰቡን ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለማራመድ ከሳውንድ ትራንዚት (Sound Transit) ጋር በቅንጅት መሥራት