ደህንነታቸው የተጠበቁ ወደ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች የዘር ፍትዓዊነት ትንታኔ

የዘር ፍትዓዊነት ራዕይ

የእኛ ራዕይ የሲያትል ትምህርት ቤት ልጆች ወደ ትምህርት ቤት በእግር የመሄድ እና ብስክሌት የመጋለብ ተሞክሮዎቸውን እንዲጀምሩ ማስቻል ሲሆን እነዚህንም ያካትታል፦

  • መዝናናት
  • የደህንነት ስሜት መሰማት
  • ከእነርሱ ማኅበረሰቦች ጋር ያሉ ግንኙነቶችን ማጠናከር
  • ለቁርስ እና ለትምህርት ወደ ትምህርት ቤት በሰዓቱ መድረስ
  • የተሻሻለ አካላዊ እና የአእምሮ ጤና

በተቋም ደረጃ የሚመራ ዘረኝነትን ለማስቆም እና ይበልጥ ፍትዓዊ የሆነች ከተማን ለመገንባት ሲያትል የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ፣ በእነዚህ ቡድኖች ውስጥ በሚገኙ ተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርገናል፦ ጥቁር ማኅበረሰቦች፣ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ማኅበረሰቦች፣ የስደተኛ እና ጥገኝነት ጠያቂ ማኅበረሰቦች፣ የአካል ጉዳት ያለባቸው ሰዎች፣ መኖሪያ አልባነትን የቀመሱ ወይም የመጠለያ ዋስትና ማጣት ችግር ያጋጠማቸው ሰዎች፣ የተመሳሳይ ጾታ ወሲባዊ ግንኙነት ፈጻሚ ሰዎችና ሌሎች ያልተለመዱ ወሲባዊ ግንኙነት ፍላጎት ያላቸው (LGBTQ) ማኅበረሰብ እና ልጃገረዶች።

ያለበትን ደረጃ ማሳወቅ

በ2018 ደህንነታቸው የተጠበቁ ወደ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች ቡድን፡

  • ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት በእግር በሚሄዱበትና ብስክሌት በሚያጋልቡበት ጊዜ የሚያጋጥማቸውን እንቅፋቶች ለመቅረፍ ደህንነታቸው የተጠበቁ ወደ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች የዘር ፍትዓዊነት ጥናትን ፈጠረ። ጥናቱ በ9 ቋንቋኧዎቸ እና በኢንላይን በራስዎ መልህክት ሳጥን ውስጥ እንደዚሁም ሰዎች በሚሰበሰቡበት ይካሄዳል።
  • ደህንነታቸው የተጠበቁ ወደ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች የዘር ፍትዓዊነት ጥናትን ለማስተዋወቅና ከትምህርት ቤት ስመለሱና ሲሄዱ የሚያጋጥማቸውን የሕይወት ተሞክሮ ለማወቅ ከተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ጋር ጥልቅ ውይይት ለማድረግ 10 ከሚሆኑ ትምህርት ቤቶች እና ቢያንስ 85% ተማሪዎቻቸው የቆዳ ቀለም አላቸው የሚባሉትን ከሚያስተናግዱ ጋር በመሆን ነው።
  • ከ50 በላይ የሚሆኑ የሕዝብ ዝግቶች በተለይ የቆዳ ቀለም ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፥ ለስደተኞች የተዘጋጁትን ተከታትዬወለሁ።
  • ደህንነታቸው የተጠበቁ ወደ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች የዘር ፍትዓዊነት ጥናትን ለማስተዋወቅና ትኩረት የተሰጠባቸው እንደ የቡድን ውይይት፥ 10 ከሚሆኑ የሕዝብ ድርጅቶች ቡና ሲጠጡ መጨዋወት ወደ 40 የህዝብ ተቋማት ጋር በመተባበር
  • በ2017 የትምህርት ዘመን ወደ 3000 ለሚሆኑ የጥናቱ ጥያቄዎችን ከአሳዳጊዎችና ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች መልስ ተቀብለናል።
  • በ2018 ገደማ ለሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የዳሰሳ ጥናት ተሳትፎን የበለጠ ተደራሽና ፍትአዊ ለማድረግ የማዳረስ ልምዳችንን እንደገና አጣርተናል።

የዘር ርትዓዊነት ትንታኔ የሥራ ሂደት

በሚቀጥለው ዓመት፣ የኛ የዘር ርትዓዊነት ትንታኔ የሚከናወነው፦

ተሟልቷል

ባለፉት ጊዜያት ማኅበረሰቦች እንዴት አገልግሎት ይሰጣቸው እንደነበረ መረጃን ሰብስቦ ትንታኔ መስጠት

2018

በውይይቶች እና ዳሰሳ ጥናቶች ተጠቅሞ በእኛ ፕሮግራም ተጽዕኖ ያረፈባቸውን ሰዎች ማሳተፍ

ወደ 40 ከሚጠጉ የህዝብ ድርጅቶች በተጨማሪ፥ በተማሪዎቻቸው የዘርና የቋንቋ ልዩነት መሰረት በተመረጡት ከሚከተሉት ትምህርት ቤቶች ጋርም እንሰራለን።

  • Aki Kurose መካከለኛ ትምህርት ቤት
  • Bailey Gatzert መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • Concord መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • Dearborn Park መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • Dunlapመለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • Rainier Beach ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • West Seattle መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
  • Wing Luke መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት

ክረምት 2019

አድስ እስትራተጂ በመንደፍ የዘር ፍትአዊነት ራዕያችንን ለመድረስ ከሕዝቡ ጋር እንሰራለን። ወደ የእኛ ራዕይ በምናደርገው ግስጋሴ ያለውን ውጤት ለመለካት መለኪያ መስፈርቶችን ለይቶ ማወቅ።

ስፕሪንግ 2019

ለማኅበረሰቦች መልሶ ሪፖርት ማድረግ

ለትምህርት ቤት የዘር ርትዓዊነት ትንታኔ ደህንነታቸው የተጠበቀ የጉዞ መሥመሮች ምን ፋይዳ አለው?

ይህ ስራ በቀጥታ የቆዳ ቀለም ያላቸው ተማሪዎችን በክፍል መገኘትን ይመለከታል ምክንያቱም ብዙ የሲያትል ተማሪዎች የትምህረት ቤት አውቶቡስ የማግኘት እድል የላቸውም። በንቃት ከትምህርት ቤቱ ጋር መነጋገር ከስኬታማ ትምህረት እና የአካላዊና አህምሮአዊ ጤና መሻሻሎች ጋር የገናኛል።

ባለፉት አራት ዐሥርት ዓመታት በታዳጊ ወጣቶች ላይ የሚያጋጥም ቅጥ ያለፈ ውፍረት በአራት እጥፍ ያክል ሲያድግ በእግራቸው የሚሄዱ እና ብስክሌት የሚጋልቡ ተማሪዎች ቊጥር በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁሏል፤ ይህም ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ጥቁር ማኅበረሰቦች ላይ ተንጸባርቆ ሊታይ ችሏል።

  • ጥቁር እና ላቲኖ ልጆች ከፍተኛ የሆነ ቅጥ ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ሲሆኑ ወደ መኪና ማቆሚያዎች፣ መጫወቻ ሜዳዎች ወይም በእግር ሊኬድባቸው ወደ የሚችሉ ጎዳናዎች በጣም ዝቅተኛ መዳረሻ ያላቸው ሆነው ይበልጥ ያታያሉ።
  • ከጥቁር ወጣቶች መካከል ወደ ¼ ገደማ በቀን ከሚመከረው አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሰዓት ያነሰ የአካል እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሲሆን ይህም ከነጭ ታዳጊ ወጣቶች ጋር ሲነጻጸር በ 13% ያክል ያነሰ ነው
  • በሲያትል ውስጥ ጥቁር ተማሪዎች የሚበዙባቸው ትምህርት ቤቶች ዝቅተኛ የሆነ በእግር የመሄድ እና በብስክሌት የመጋለብ መጠን ያላቸው ሲሆኑ ከነጭ ተማሪዎች አንጻር በ 50% ያነሰ ነው

በተከታታይ ሳያቋርጡ ወደ ትምህርት ቤት ከትምህርት ቤት በእግር መመላለስ ዘለቄታ ያለው የጤና ጥቅም የሚያስገኝ ሲሆን ከሚከተሉት ጋር ግንኙነት ካለው በታዳጊ ወጣቶች ላይ የሚያጋጥም ቅጥ ያጣ ውፍረት ተጋላጭነትን ሊቀንስ ይችላል፦

  • የልብና የደምሥሮች (cardiovascular) በሽታ
  • የስኳር በሽታ
  • ካንሰር
  • ስትሮክ (stroke)

ተጨማሪ አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በተጨማሪ የተሻሻለ የአእምሮ እና የአካል ብቃት ጤና እና አካዳሚያዊ ስኬት ወደ ማግኘት ሊያመራ ይችላል።

አጠቃላይ ሐሳብ

Happy kid on bike with adult helping

የስያትል የዘርና የማህበራዊ ፍትህ ንቅናቄ (RSJI) በከተማ አስተዳደር ውስጥ ያለውን ተቋማዊ ዘረኝነትና በዘር ላይ የተመሰረቱ አድሎ ለማስቆም የሚደረገው ከተማ-አቀፍ ጥረት ነው፡፡ የዘር ፍትዓዊነት ቱልኪት (RET) የዘር ፍትዓዊነት ተጽንኦዎችን ለመቅረፍ በምደረገው እንቅስቃሴ ፖሊሲዎችን፣ ንቅናቄዎችን፣ ፕሮግራሞችን እና የባጀት ጉዳዮችን ለመምራት መደበኛ ሂደትንና ጥያቄዎችን ያስቀምጣል፡፡

ደህንነታቸው የተጠበቀ ወዴ ትምህርት ቤት የጉዞ መሥመሮች (SRTS) ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ሲጓዙ እና በብስክለት መጋለብ ቀላልና ደህንነቱ የተጠበቀ የሚያደርግ አከባቢያዊ፣ ሀገራዊ እና ብሔራዊ እንቅስቃሴ ነው፡፡ የስያትል ተራንስፖርት መምሪያ ይህንን ግብ ለማሳካት የስልቶቹን ቅንጅት ይጠቀማል፡

  • ትምህርት: እያንዳንዱ ሰወ እንዴት ደህንነቱን ጠብቆ መጓዝ እንደሚችል ማወቁን ማረጋገጥ
  • ማበረታታት: በትምህርት ቤት ማኅበረሰብ ውስጥ በእግር መሄድን እና ብስክሌት መጋለብን ማበረታታት
  • ምሕንድስና: እንደ የእግረኛ መንገዶች፣ ለደህንነት አስተማማኝ የሆኑ ማቋረጫ መንገዶች፣ እና ብስክሌት ለመጋለብ የተሻሻሉ መንገዶችን የመሳሰሉ የግንባታ ፕሮጄክቶች
  • ሕግ ማስከበር: የትራፊክ ደህንነት ሕጎችን ለማስከበር ከሲያትል የፖሊስ መምሪያ ጋር በአጋርነት መሥራት
  • ምዘና: በእኛ የተጋሩ የደህንነት ግቦች ላይ ያለውን ግስጋሴ ዱካ ክትትል ማድረግ
  • ማብቃት: ለምርጥ ትምህርት ቤቶች ግብዓቶችን ማቅረብ

Transportation

Greg Spotts, Director
Address: 700 5th Ave, Suite 3800, Seattle, WA, 98104
Mailing Address: PO Box 34996, Seattle, WA, 98124-4996
Phone: (206) 684-7623
684-Road@seattle.gov

Newsletter Updates

Subscribe

Sign up for the latest updates from Transportation

The Seattle Department of Transportation (SDOT) is on a mission to deliver a transportation system that provides safe and affordable access to places and opportunities for everyone as we work to achieve our vision of Seattle as a thriving, equitable community powered by dependable transportation.